HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

ወጣቶች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ያሰባሰቡትን ድጋፍ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረከቡ

February 17, 2021Uncategorized

የቀድሞ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የኢትዮጵያ ወጣት ለሰላም ማህበር በትግራይ ክልል በግጭት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ያሰባሰቡትን ድጋፍ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አስረክበዋል፡፡ የካቲት 4 ቀን 2013 ዓ.ም በማህበሩ በኩል ለተጎጂዎች በቀጥታ እንዲደረርስ የተሰጠው ድጋፍ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመትና የምግብ፣ የአልባሳት፣ የህጻናት አልሚ ምግቦችና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የቀድሞ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመወከል ድጋፉን ያስረከቡት አቶ አቢዮት በላቸው ‹‹ይህንን ድጋፍ ያደረግነው ለትግራይ ህዝብ ያለንን ወገናዊነት ለመግለጽ ነው›› ብለዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህን መሰል ድጋፍ ለማድረግ የተሳተፉትን ጓደኞቻቸውንና የኢትዮጵያ ወጣት ለሰላምና ለልማት ማህበር አባላትና በጎ ፈቃደኞችን አመስግነዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወጣት ለሰላምና ለልማት ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ቦና ደበላ በበኩላቸው ‹‹የቀድሞ የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ጥሪ ተቀብለን አባላቶቻችንንና በጎ ፈቃደኞቻችንን በማስተባበር ይህንን ድጋፍ ማድረግ በመቻላችን ደስታ ተሰምቶኛል፡፡›› ብለዋል፡፡ አያይዘውም በቀጣይም በሁሉም የሃገራችን አካባቢዎች በተለያዩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለመደገፍ አቅማቸው የፈቀደውን ሁሉ በማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በኩል ድጋፉን የተረከቡት የማኅበሩ ምክትል ዋና ፀሐፊ አቶ እንግዳ ማንደፍሮ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው በራስ ተነሳሽነት የሚደረጉ መሰል ድጋፎች አጋርነትን ከማሳየት ባለፈ እንደ ሃገር ችግሮችን በራስ አቅም ለመፍታት ለሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል፡፡ አቶ እንግዳ አክለውም ሌሎች የማህበረሠቡ ክፍሎች በተለያዩ የሃገራችን አካባቢዎች በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ለመደገፍ እጆቻቸውን እንዲዘረጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከለጋሾች የተበረከተው ድጋፍ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አማካኝነት ለሚመለከታቸው ተጎጂዎች በቀጥታ እንደሚደርስ ማኅበሩ ገልጿል፡፡

በቀጣይ መርዳት ለምትፈልጉ፡- በኢ.ቀ.መ.ማ የባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000327016559 (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) በኩል ማገዝ ይችላሉ፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System