HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

ኢቀመማ የህብረተሰቡን አደጋ የመቋቋም አቅም ለመገንባት የሰራቸው ሥራዎች አበረታች እንደነበሩ አስታወቀ

September 10, 2018Uncategorized

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር (ኢቀመማ) ነሀሴ 25 ቀን 2011 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በ2010 የበጀት ዓመት ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ለሆኑ የህብረተሰቡ ክፍሎች የአደጋ ምላሽ እና ከአደጋ በኋላ የማቋቋም ሥራዎችን አከናውኗል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለ297 ሺህ አባዎራዎች የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ ድጋፍ ለመስጠት በማቀድ 599 ሺህ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ በማድረግ እቅዱን ከእጥፍ በላይ ማሳካት ችሏል፡፡

ማኅበሩ በምዕራብ ጉጂና ጌዲኦ፣ በጅግጅጋ፣ በሶማሊያ፣ ኦሮሚያ እና በሌሎች በተለያዩ አካባቢዎች የደረሱ ግጭችን ተከትሎ ለተፈናቀሉ ወገኖች ምግብ እና ምግብ ነክ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል፡፡

ኢቀመማ ህብረተሰቡን ከአደጋ በኋላ ለማቋቋም በዘረጋቸው 9 ፕሮጀክቶች አማካኝነት ከ28 ሺህ 500 በላይ አባወራዎች (142 500) በላይ ሰዎችን በመደገፍ የዕቅዱን 99 በመቶ እንዳስፈፀመ አስታውቋል፡፡ አደጋን አስቀድሞ በመከላከል እና በተለያዩ የልማት ተግባራት ማለትም የግብርና ሥራ እና የምርጥ ዘር አቅርቦት፣ የኑሮ ማሻሻያ እና የአቅም ማጠናከሪያ ሥራዎች፣ የጤና እና ንፅህና አጠባበቅ ድጋፎች፣ መሰረታዊ መድሃኒቶችን ማሰራጨት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ጉባኤው ሌሎች በበጀት ዓመቱ ታቅደው የነበሩ ተግባራትንና አፈፃፀማቸውን በመገምገም መሻሻል እና ተጠናክሮ መቀጠል ይገባቸዋል የተባሉ ጉዳዮችን ለመለየት ያስቻለ ሲሆን፤ የትኩረት አቅጣጫዎችን አመላክቷል፡፡ የአደጋ ጊዜ የመጠባበቂያ ቁሳቁስ በሚፈለገው መጠን በመጋዘን አለመያዝ በዓመቱ ካጋጠሙ ችግሮች መካከል ተጠቅሷል፡፡ የቅንጅትና የትብብር ሥራ፣ አቅም ግንባታ እና ወጪ ቅነሳ ማህበሩ በቀጣይ ትኩረት የሚያደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ለክልሉ የቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በየዓመቱ የ500 ሺህ ብር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑ የሚበረታታ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ በበጀት ዓመቱ ለህብረተሰቡ ፈጥኖ በመድረስ እና አደጋን በመከላከል በኩል የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ክቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የዕውቅና ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፤ ከትላልቅ ክልሎች አማራ እና ኦሮሚያ፤ ከታዳጊ ክልሎች የቤኒሻንጉል እና ሀረሪ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡

በጠቅላላ ጉባኤው ከብሄራዊ ፅ/ቤት እና ክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የክልል እና ብሔራዊ ቦርድ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡ በተጨማሪም የሞያሌ ልዩ ወረዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በስብሰባው ላይ በልዩ ሁኔታ ተገኝቷል፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System