HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

ኮካ ኮላ ኩባንያ ለማኀበሩ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

April 7, 2020Uncategorized

በሀገራችን ከፍተኛ አደጋ አየጋረጠ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ አ.ማ /ኮካ ኮላ ኩባንያ/ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፡፡

መጋቢት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ድጋፉን አስመልክቶ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የኮሮና ቫይረስ ዜናን በፈረንጆቹ ታህሳስ 2019 ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ ቫይረሱ በህዝባችን ላይ ሊያደርስ የሚችለውን አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ዝግጅት እያደረገ መቆየቱን የገለፁት የማኀበሩ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር መሸሻ ሸዋረጋ፣ በተለይም ታዋቂ የሀገሪቷ አርቲስቶችን፣ የኢትዮ ጃዝ ሙዚቃ ፈጣሪ ዶ/ር ሙላቱ አስታጥቄ፣ ደራሲ አያልነህ ሙላቱ፣ አርቲሰት አለማየሁ እሸቴ፣ ፋንቱ ማንዶየ፣ ንዋይ ደበበንና አረጋኸኝ ወራሽን እንዲሁም በሲኒማ ኢንደስትሪው ታዋቂ የሆነውን አርቲስት መኮንን ለአከን በመያዝ በከተማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ላይ ከፍተኛ የማኀበራዊ ንቅናቄ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

ዋና ፀሐፊው ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ኩባንያ ማኀበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለማኀበሩ ይህንን የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው ድጋፉን አስመልክተው በመላው የቀይ መስቀል አባላቶችና በጐ ፈቃደኞች ስም አመስግነዋል፡፡ ወደፊትም ኩባንያው ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋቸውን  ገልፀዋል፡፡

ማህበሩ የተገኘውን የገንዘብ እርዳታ በተለይም ከፍተኛ ቁጥር ላላቸው በመዲናዋ ጐዳናዎች ላይ ወድቀው ለሚገኙ ወጣቶች፣ ሴቶችና አዛውንቶች የምግብ ድጋፍ እንደሚውልም ተመልክቷል፡፡

በኢትዮጵያ የኮካ ኮላ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዳረል ዊልሰን በበኩላቸው ኮሮና ቫይረስ በዓለማችን ታሪክ ከአሁን ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሰብዓዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን አመልክተው ኩባንያቸው ችግሩን ከግምት በመውሰድ ድጋፍ ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን አቅም በፈቀደ ሁኔታ ከጎናቸው እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ጋር አያይዘው ኩባንያቸው የእጅ ማጽጃ ሳኒታይዘሮችንም ማምረትና ማከፍፈል እንደሚጀምር ገልፀው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቫይረሱን በትብብር ለመግታት እንዲቻል ሀኪሞች የሚሰጡትን መመሪያ መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ልክ እንደ አሁን ቀደሙ ሁሉ ወደፊትም ከኢትዮያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመልክቷል፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System