HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

ለእየሩሳሌም መታሠቢያ ድርጅት በግጭት ለተጎዱ ወገኖች የ500 ሺ ብር ድጋፍ አበረከተ

March 3, 2021Uncategorized

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት በትግራይና በመተከል በግጭት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ የሚሆን የ500 ሺ ብር ስጦታ ሐሙስ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም ለኢትጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አስረክበዋል፡፡

መታሰቢያ ድርጅቱን በመወከል ስጦታውን ያስረከቡት የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ሊቀመንበር በኩረ ምዕመናን ጌታሁን በሻህ እንደተናገሩት ማህበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የልማትና የሰብዓዊነት ተግባራትን ሲያከናውን የቆየ መሆኑን ገልጸው በአሁኑ ወቅት በግጭት ምክንያት በችግር ውስጥ የሚገኙ የትግራይና መተከል ወገኖቻችን ጉዳይ ስላሳሰበን ይህን ድጋፍ አድርገናል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ዋና ፀሐፊ አቶ ጌታቸው ታዓ በበኩላቸው ማኅበሩ በተለያዩ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለመደገፍ በሚያደርገው ጥረት የግብረሰናይ ማህበራት፣ ግለሰቦች ፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው በዛሬው ዕለትም በትግራይና በመተከል የሚገኙ ተጎጂ ወገኖቻችንን ለመደገፍ ማህበራችን ላደረገው ጥሪ ምላሽ በመስጠት ይህንን ድጋፍ ያደረገውን ለኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት አመስግነዋል፡፡

አቶ ጌታቸው አያይዘውም ይህንን አርአያ በመከተል በአገር ውስጥና በውጪ የሚኖሩ የሰብዓዊነት ወዳጆች እገዛቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡

እርዳታ ማድረግ ለምትፈልጉ ፡- • በኢ.ቀ.መ.ማ የባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000327016559 (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ወይም

                                 • የሰብአዊነት ድጋፍ ፈንድ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1 000 000 902 008 በኩል ማገዝ ይችላሉ፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System