HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ በአጭር የሞባይል መልዕክት የአባላት ምዝገባ ሊጀምር ነው

February 18, 2019Uncategorized
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ 6546 አጭር የፅሁፍ መልዕክትን በመጠቀም የአባላት ምዝገባ እና የእርዳታ ማሰባሰብ ስራዎችን ሊጀምር ነው፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ይህን ይፋ ያደረገው የካቲት 05 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡
 
የቅርንጫፉ ኃላፊ አቶ አበባው በቀለ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ላለፉት 38 ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረው የቤት ለቤት የአባላት ምዝገባ ዘዴ ኋላ ቀር በመሆኑ ይህን አጭር የፅሁፍ መልዕክት መጀመር በርካታ ሰዎች አባል እንዲሆኑና የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
 
ዶ/ር ሚርጌሳ ካባ የቅርንጫፉ ቦርድ ሊቀመንበር በበኩላቸው፣ አዲስ አበባ የተለያዩ ሀገራዊና አለምአቀፋዊ ተቋማት መቀመጫ መሆኗን ገልፀው አጭር የፅሁፍ መልዕክቱን መጠቀም የቅርንጫፉን አባላት ቁጥር ለመጨመር እና ሀብት ለማሰባሰብ የተሻለ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ኢትዮ ቴሌኮም ላደረገው ድጋፍ የቦርድ ሊቀመንበሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
 
ማንኛውም ሰው በ6546 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ያለምንም ክፍያ ከተመዘገበ በኋላ በ6547 አባል ሆኖ መመዝገብ እንዲሁም በ6548 ደግሞ የፈለገውን መዋጮ በማድረግ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሚያከናውናቸውን ሰብዓዊ ተግባራት ማገዝ እንደሚቻል ታውቋል፡፡
 
አጭር የፅሁፍ መልዕክቱ አገልግሎት ከሳምንት በኋላ በይፋ እንደሚጀምር በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ተገልጿል፡፡
 
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ካሉት አጠቃላይ 6.1 ሚሊዮን አባላት ውስጥ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ወደ ሁለት መቶ ሺህ አባላት እንዳሉት አቶ አበባው ገልፀዋል፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System