HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በመላው ሀገራችን የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተሳተፈ ነው

July 26, 2021Uncategorized

ቅዳሜ ሐምሌ 17 ቀን 2013 ዓ.ም ከ 300 በላይ የሚሆኑ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ዋና መ/ቤት እና የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሠራተኞች፣ በጎ ፈቃደኞችና አባላት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ስሙ ኮዬፈጬ አደባባይ ተብሎ ሠራተኞች፣ በጎ ፈቃደኞችና አባላት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ስሙ ኮዬፈጬ አደባባይ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ችግኞችን ተክለዋል፡፡

በዕለቱ በቦታው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ዋና ፀሐፊ አቶ ጌታቸው ታዓ እንደተናገሩት ማህበሩ ከአደጋ ምላሽ ስራዎች ጎን ለጎን የሰው ልጆችን ህይወት በዘላቂነት ለማሻሻል የሚያግዙ የልማት ተግባራትንም ያከናውናል፤ በተለይም የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎች ላይ መሳተፍ ቀይ መስቀል ከተቋቋመለት የሰው ልጆችን ስቃይ የመቀነስ ዓላማ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ በመሆኑ በባለቤትነት ስሜት ትኩረት ሰጥተን የምናከናውነው ተግባር ነው ብለዋል፡፡

የደን ልማትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስና የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው ሲሆን በሃገራችን ተከስተው የነበሩትን ድርቅና ረሃብ፤ እንዲሁም የተፈጥሮ አካባቢ መራቆትን ለመግታት ከ1970ዎቹ ጀምሮ የማህበሩ በጎፈቃደኞች፣ አባላትና ሠራተኞች በወሎ፣ በትግራይ፣ በጎጃምና በሌሎችም የሃገሪቱ አካባቢዎች ችግኞችን በመትከል በደን ልማትና የአካባቢ ጥበቃ ስራ ላይ አዎንታዊ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡

በዘንድሮው መርሃ ግብር በሁሉም ክልሎች የሚገኙ፤ የማኅበሩ ሠራተኞች፣ አባላት እና በጎ ፈቃደኞች በዚህ የኢትዮጵያን እናልብሳት ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System