HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Providing Trainings
    • Consultancy Services
    • Catering & Lodging Service
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

19ኛው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ

July 29, 2022Uncategorized
“ያለፉት ሦስት አመታት ሕዝባችንና አገራችን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የነበርንበትና እና ከዚህም ውስጥ ለመውጣት በጋራ ትግል ያደረግንበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ጉዞ ውስጥ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ የዜጎችን ህይወት ታድጓል፣ የተከፉትን፣ ልባቸው የተሰበረ ቤተሰቦችን አንገት ቀና ለማድረግ ችሏል፡፡” ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የማኅበሩ የበላይ ጠባቂ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ካደረጉት ንግግር (ሐምሌ 9/2014) በጠቅላላው ጉባዔ ላይ በተደረገው የአመራር ቦርድ አባላት ምርጫ አምስት በድጋሚ፣ አራት አዲስ ተመርጠዋል፡፡ በድጋሚ የተመረጡት የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ቶላ ቀደም ሲል ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር፡- “የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ሁልጊዜ ቅድሚያ ለሰብኣዊነት የሚለውን መርህ አጥብቆ ያራምዳል፡፡ በዚህ መርህ ዙሪያ ያጠነጠነ ክንውንም ያደርጋል፡፡ ለምናደርገው መልካም ነገር፣ ለሚሰማን ፍቅርና መልካም ስሜት እንዲሁም በደስታና ፍሰሃ የሚሞላውም የኛ አእምሮና አካል ነው፡፡ ለዚህም የተሳካ ጉዞ የማህበሩ ሰራተኞች፣ በጎፈቃደኞች፣ አባላት፣ መንግስት፣አጋሮቻችን፣ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ አካላት ዋናዎቹ የስኬታችን ባለቤቶች ናቸው፡፡ “ ብለዋል፡፡ ጠቅላላ ጉባዔው ላይ 250 ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን 173 ቱ ከክልል የቀይ መስቀል ቅርንጫፎች የመጡ ናቸው፡፡ ማኅበሩን ለሚቀጥሉት አራት አመታት እንዲመሩ የተመረጡት የኢቀመማ የአመራር ቦርድ አባላት የሚከተሉት ናቸው፡
1. አቶ አበራ ቶላ፣ ፕሬዚዳንት
2. ዶ/ር ፎዚያ አሚን፣ ምክትል ፕሬዚዳንት
3. ወ/ሮ ሒክመት አብደላ፣ አቃቤ ነዋይ
4. ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፣ አባል
5. ፕሮፌሰር አብርሃም ኃ/አምላክ፣ አባል
6. አምባሳደር ዶ/ር ቶፊቅ አብዱላሂ፣ አባል
7. ዶ/ር አዲስአለም ሙላት፣ አባል(የወጣቶች ተወካይ)
8. ኢንጂነር ጌታሁን ሁሴን፣ አባል
9. ዶ/ር ሰይፉ ጌታሁን፣ አባል
May be an image of 4 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 4 people, people sitting and people standing

 

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society Triaining Institute

Quick Links

  • Book a Training Room
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System