Join our Telegram channel @ethiopianredcrosstraining.
  • Register for Training
  • Book Training Facilities
HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Trainings Services
    • Consultancy Services
    • Training Facility Services
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
    • Catering & Lodging Service
    • Fitness & Wellness Service
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Call for training
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

የማኅበሩ ሠራተኞች በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከአዲሱ ዋና ፀሀፊ ጋር ተወያዩ

March 3, 2021Uncategorized

                                                                       ጥር 17፣ 2013 ዓ.ም ዋና ፀኃፊ ሆነው በድጋሚ ወደ ማኅበሩን የተቀላቀሉት አቶ ጌታቸው ታዓ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡

 

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል የዋናው ፅህፈት ቤት ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም በማኅበሩ ማሠልጠኛ ማዕከል ከዋና ፀኃፊ አቶ ጌታቸው ታዓ ጋር ባካሄዱት የትውውቅ እና የምክክር መድረክ ማኅበሩን በሚመለከት ትኩረት ይፈልጋሉ ያሉዋቸው ጉዳዮችን አንስተው በጋራ መክረዋል፡፡

በመድረኩ ላይ ትውውቅ ያደረጉት አቶ ጌታቸው ታዓ፤ ከ1993-1997 ማኅበሩን በኃላፊነት መምራታቸውን እና በቀጣይም በዓለም ዓቀፉ የቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ፈዴሬሽን ውስጥ በልዩ ልዩ ኃላፊነቶች ላይ የተለያዩ አገራት በመዘዋወር ሠብዓዊነትን ሲያገለግሉ እንደቆዩ አስታውሰዋል፡፡ በመጨረሻም በዘርፉ ያካበቱትን ጠቃሚ እውቀት እና ልምድ ይዘው ሠብዓዊነትን አንድ ብሎ ወዳስጀመራቸው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል በመመለሳቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡ ዋና ፀኃፊው አክለውም ያላቸውን ሙሉ አቅም እና ግዜ ተጠቅመው የማኅበሩን አገልግሎት እና ተደራሽነት ለማሻሻል እንደሚተጉ አስረድተው፤ ለሚጠበቀው የጋራ ውጤት ሁሉም የማኅበሩ ባልደረቦች በኃላፊነት ስሜት ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

በመድረኩ ከሠራተኞች እና ከሌሎች ሥራ ኃላፊዎች የማኅበሩን ሥራ እንቅስቃሴ የተመለከቱ የተለያዩ ጉዳዮች ተነስተው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በጎ ፈቃደኞች እና አባላት ፣ የአምቡላንስ አገልግሎት እና የማኅበሩ ሀብት አሰባሰብ ትኩረት ካገኙ ሀሳቦች መካከል ናቸው፡፡ ማኅበሩ በበጎፈቃደኞች እና አባላት ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ የምልመላ እና አስተዳደር ሥራው ቀዳሚ ትኩረት እንደሚሰጠው በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል፡፡

ማኅበሩ ከሚያከናውናቸው ሠብዓዊ ተግባራት መካከል የአምቡላንስ አገልግሎት ዋነኛው ነው፡፡ ከቅርብ ግዜ ወዲህ በሀገሪቱ የተፈጠሩ ግጭቶችን ተከትሎ የወደሙ እና የት እንዳሉ የማይታወቅ ጥቂት የማይባሉ አምቡላንሶች እንዳሉ፤ ሁኔታው ማኅበሩ የሚከተላቸውን መርሆዎች መሠረት አድርጎ የሚሠጠውን አገልግሎት እንዲስተጓጎል አድርጓል፡፡ ችግሩን በመሠረታዊነት ለመቅረፍ ትምህርተ ቀይ መስቀል ከታች ለሚገኘው የመንግስት መዋቅር እና ለሚመለከታቸው የህብረተሰቡ ክፍሎች አጠናክሮ መስጠት እንደሚገባ ዋና ፀሀፊው አመላክተዋል፡፡

በመጨረሻም ማኅበሩ የቆመለትን ዋና ዓላማ ‹ሰብዓዊነት› ማዕከል በማድረግ በተፈጥሮም ሆነ ሠው ሰራሽ አደጋዎች ጉዳት ለሚደርስባቸው ወገኖች ያለምንም ልዩነት ህዝብን ለማገልገል ቃል በመግባት ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

Add Comment Cancel


Recent Posts

  • Hello world!
  • “በአለም አቀፍ ደረጃ የርሃብ አደጋ በአስከፊ ሁኔታ ሊባባስ ይችላል” – የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ቀይ ጨረቃ ንቅናቄ
  • The Ethiopian Red Cross Society is evacuating residents at risk of flooding in the Afar region
  • Five districts of the Afar region suspected of flooding
  • Society receives vehicles worth more than Birr 70 million

Recent Comments

  1. A WordPress Commenter on Hello world!

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society CCDHS [Training Institute], Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ERCS-TI@redcrosseth.org

Ethiopian Red Cross Society CCDHS [Triaining Institute]

Quick Links

  • Book Training Facilities
  • Register for Training
  • Book Now
  • Call for training
  • Trainings Services
  • Training Catalogue
  • Telegram
  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Flickr
Copyright ©2026 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System